Thursday, May 16, 2013

Ethiopia and Sudan concur to stop EPPF -

Representatives from four bordering states in Ethiopia and Sudan have agreed to work closely to prevent cross-border activities of EPPF  in a meeting between the two sides.
Authorities in Amhara regional state said on Tuesday that the joint meeting, which aimed at further fostering multilateral cooperation along the common border, was held in north Ethiopia’s Gonder city.
Administrators of the two sides agreed to jointly combat EPPF's activities along the shared border.
Addressing participants at the meeting, the administrator of North Gonder zone, Gizat Abiyu, said that joint cooperation between the bordering states is playing a crucial role in enhancing the historic ties between the two East African countries.
Following the meeting, both sides vowed to implement a common agreement covering border zones.
Administrators from Ethiopia’s Gonder, Gurishan, Basonda and Doca zones, as well as Dinder in Sudan’s Gedarif area took part in the joint meeting.
Addis Ababa and Khartoum already have various cooperation agreements at both state and regional levels which are based on mutual interest of stopping opposition on both sides.

Joint cooperation activities in recent years have also witnessed a stronger partnership between the countries in many areas.
The two neighbors have signed a number of cooperation agreements on political, socio-economic and security matters, as well as on EPPF and other liberation movements activities.
Authorities in both countries say joint cooperation and security measures in adjacent regions of Ethiopia and Sudan have succeeded in ensuring the continuity of both dictatorial regimes.
The countries have also seemingly  managed to control cross-border attacks by EPPF  elements in their respective nations.

Wednesday, January 9, 2013

መምህሩ እንደ እረኛ ተማሪው እንደ መንጋ! -ታደለ መኩሪያ tadele@shaw.ca

መምህሩ እንደ እረኛ ተማሪው እንደ መንጋ!
እንዲህ ያለ ዘመን ፣ዘመነ ጋንድያ፤
ሰው እንዴት ይሆናል፣ ከርሞ እንዳ ጥጃ፤
በሃገራችን  ትምህርታቸውን የሚያቋርጡ  ተማሪዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑ ይገለፃል። ይህንንም ለማስቆም በትምህርቱ
ዓመት  መጀመሪያ ላይ የተመዘገቡትን ተማሪዎች ቁጥር መምህራን ተረክበው በዓመቱ መጨረሻ  ማስረከብ እንዳለባቸው
ለመፍትሔነት  ቀርቧል። መምህራንም የደረጃ  እድገት፣
የደመወዝ ጭማሪ  ለማግኘት የተረከቧቸውን ተማሪዎች ቁጥር
ሳይቀነሱ ማስረከብ እንደሆነ  ተገልጿል።
ይህን ዓይነት ቁጥጥር በሰሜን ኮሪያ ‘labor Camp’ እሥር
ቤቶች መሰል ጣቢያዎች በተቋቋሙ ትምሀርት ቤቶች
የሚሠራበት  መመሪያ ነው። ይህ ዓይነት መመሪያ
በማስተማርና በመማር ሥራው ላይ አደጋ አለው። መምህራን
ከቀለም አባትነታቸው ይልቅ ያለተማሪው ፍላጎት
ተቆጣጣሪዎች ያደርጋቸዋል።በሰባዐዊ መብት ገፋፊት
ያስፈርጃቸዋል።ተማሪዎችም  ቢሆኑ መብታቸውን የገፈፈውን
መምህር ለብቀላ  ለወያኔ እንዲሰልሉት መንገድ ይከፍታል።
ይህ ድርጊት በሰሜን ኮሪያ እየተሠራበት ነው። ለግንዛቤ ያህል በአንድ ወቅት የሰባዐዊ መብት ተከራካሪ  ተማኝ በየነ መለስ
ዜናዊ ከመሞቱ ሰምንት ወር ቀደም ብሎ እንዲህ ብሎ ነበር፤  ‘ጠቅላይ ሚስትር መለስ ዜናዊ  ቢሞት፣ እንደሰሜን ኮሪያን
ሕዝብ ለኬሚን ሱንግ አስገድደው  እንዳስለቀሱት፤ መለስ ቢሞት  ወያኔ መላውን  የኢትየጵያን ሕዝብ ያስለቅሱታል’  ያለው
ትንቢተ ደረሰ። ይህ አሁን ወያኔ ትምህርትን አስመልክቶ እያደራ ያለው ድር  የዘርና የጎሣው ክፍፍል ሌላው አካል ነው።
አንዳንድ በውጭ የሚኖሩ በጎ አሳቢ ‘wishful thinkers’  መሰል ምሁራን እኛ ስለፖለቲካው አያገባንም፣ ግን ስለትምህርት
እድገት ምርምር አድርገን የትምህርቱ ሥራ ግቡን እንዲመታ አስተዋጾ እናደርጋለን ሲሉ ይደመጣሉ። ‘ለሥጋው ጾመኛ ነኝ፣
ከመረቁ ሰጡኝ’ አባባል ይመስላል። ‘እንኳን አቺን የዝንብ ጠንጋራ አናውቃለን’ ይላል የሃገሬ ስው! የወያኔ ፖለቲካ
ያልገባበትና ሊቆጣጠረው የማይፈልገው መሥሪያ ቤት ወይም የሥራ መስክ የቱ ነው?  ሕዝብን እርስ በርሱ  ማናከሱ አንሶት
በትምህርቱ  መስክ አዲስ ደባ አቅዷል። መምሀሩም ተማሪውም  በአንድነት እንቢኝ ማለት ይጠበቅባቸዋል።
ከዚህ ቀደም የትምህርቱን ሥራ አስመልክቶ  በድህረ ገጾች ሁለት መጣጣፎች አድርጌ ነበር።’ በድንቁርና ላይ ወሮሸባ እንበል’
እና ‘መምህሩም ያስተምር ተማሪውም ይማር’ የሚሉ ነበሩ። ጠቅላላ ይዘታቸው የትምሀርቱን ሥራ አስመልክቶ በባለቤትነት
ሕበረተሰቡ መምከር እንዳለበት ጦቁሜለሁ። የትምህርቱ ሥራና የፖለቲካው ሥራ ለየቅል መሆናቸውን ለማሳየት ሞክሬለሁ፤
ዜጎች የሚጎዳቸውን ከሚጠቅማቸው ለይተው የሕይወታቸው መመሪያ ለመንደፍ ትምህርት አማራጭ የሌለው መሣሪያ
እንደሆነም ገልጫለሁ። ልጆቻቸው ተኮትኩተው የሚያድጉበትን ሥረዓተ ትምህርት ለመቅረጽ ሐሣብን በነፃነት መግለጽ
ቅድሚያ  የሌለው ቅድሚያ መሆኑን ጠቁሜአለሁ። የዓለም ሕብረተሰብም ይህንን አውቆ  የማወቅና የማሳወቅ መብት ፍጹም
ያልተገደበ ነው። በእኛ ሃገር የሕብረተሰቡ አካል የሆኑት መምህራንና ተማሪዎች ሐሣባቸውን ሲገልጹ ሲታሰሩና ሲገደሉ ነው
ያየነው።የወያኔ መንግሥት የትምህርት ሥራው ማሽቆልቆሉንና የተማሪው ለትምሀርት ያለው ፍላጎት እየቀነሰ መምጣቱን አሌ
የሚለው አይደለም። ምክንያቱንም አያውቀውም ማለት አይቻልም። ለተማሪው የመማር ፍላጎት ማጣት የትምህርት ሥራው
ውጤት ማሽቆልቆል መምህራንና ተማሪዎችን ተጠያቂ ማድረግ ቂልነት ነው። ሐቁን  ግን ሰው ያወቀው ፀሐይ የሞቀው ነው።
ለተማሪው ትምሀርት ማቋረጥ ሆነ ለትምህርቱ ማሽቆልቆል ተጠያቂው በመሣሪያና በስለላ ኃይሉ ጉልበቱን አፈርጥም
በማያውቀው የትምህርቱ ሥራ ላይ የሚቦራጨቀው ወያኔ ብቻ ነው።
ስለመገናኛ ብዙሃን ለትምሀርቱ ሥራ የቱን ያህል አስተዋጾ እንደላቸው ባለፈው ጹሑፌ ጦቅሜ ነበር። ከሃገር ቤት በኢ ሜ ል
የደረሱኝ መልክቶች ‘አንተ የደላህ ነህ ሙቅ ታኝካለህ’ መሰል ነበሩ። ሌላው ቀርቶ እንደቀድሞ ዓመታት ተማሪዎቹን
የሚያቃቁ ተግባሮች ከአንደኛ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ አይተዩም፤ ሌላው ቀርቶ  በትምህርት ቤቶች መጫወቻ ኳስ የለም ፣
ተማሪውም ሆነ አስተማሪው ኳስ የሚጫወቱባቸውን ትጥቅ ማሟላት አይችሉም፤ ተማሪ በጠኔ የሚወድቅበተ ሃገር እኮ ነው
ያለን እያሉ   ኢ ሜ ል አድርገወልኛል።መጫወቻ ሜዳዎች ቁሻሻ ለብሰዋል፣ የድራማ፣ የክርክር፡ የሰፓርት ውድድር  የሳይንስ
፣ የዛፍ ተከላ፣ የወላጅ ቀን፣ሁሉም የሉም። ዩኒቭርሲቲ ተከፈተ እንጂ አንደኛ ደረጃና ሁለተኛ ደረጃ ተገነባ ሲባል የሰማ አለ?
የቀድሞቹስ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች  የተማሪዎች መቀመጫ አላቸው። አንደንድ ትምህርት ቤቶች ተንደው
ሕፃናት ዳስ በመሰሉ ቤቶች ውስጥ ትምህርታቸውን የሚከታተሉ አሉ፤ በዙዎቹ አቋርጠው ይሄዳሉ። በኦሮሚያ ኦቢዲዎ
አስተዳደር ስንት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተገነቡ? የነበሩት ፈርሰው እንደሆን እንጂ አንድም አልተሠራም።
ሕብረተሰቦች በቋንቋቸው እንዲማሩ ተደርገዋል ተብሏል። በቂ መጽሐፍቶች በተባለው ቋንቋ ጥራታቸውን  ጠብቀው
ቀርበዋል? የሕብረተሰቡን ፍላጎትስ የሚያጸባርቁ ናቸው? ይህን ሆድ ይፍጀው። ቋንቋችን ተከበረ ባሕላችን ታወቀ የሚሉት
አፍቃሪ ወያኔዎች፤ ሐቁ ልጆቻቸውን ትልልቅ ከተማዎች ልከው የሚያስተምሩ ናቸው። ያውም በሚያወግዙት ቋንቋ፤
የሚወክሉትን ሕዝብ ግን ባልተሟላ የትምህርት መሣሪያና  ባልተጠና  ሥረዓት ትምህርት ያደነቁሩታል። ተማሪው
ትምህርቱን ቢያቋርጥ እንዴት ይፈረድበታል? መምህሩስ እንዴት ማስቆም ይቻለዋል?
ዛሬ ተማሪን እንደመንጋ  መምህሩንም እንደ እረኛ በሆነበት አካባቢ የመማርና የማስተማር ጣምና ለዛ የሌለው መራራ ነው።
የዕውቀት ገበታ ሊሆን አይችልም።
ሃገርንና ራሱን የፈጠረ ሕዝብ የሚበጀውን ከራሱ በላይ የሚያውቅለት የለም እና ማንነቱ ከመጥፋቱ በፊት ከዕንቅልፉ መነሣት
አለበት። መምህሩንና ተማሪውን ተጠያቂ ማድረግ ከሐላፊነት ከመሸሽ ሌላ የሚፈይደው ነገር የለም።    
ዓምላክ ኢትዮጵያን ይታደጋት!
ታደለ መኩሪያ
tadele@shaw.ca

Monday, December 3, 2012

የተኩላው ለምድ ሲገፈፍ!!!

በበላይ ወንዳፍራሽ













ይህ ወቅት በሃገራችን ኢትዮጵያ አንዳች ለውጥ ሊመጣ በዋዜማው ላይ እንገኛለን።ይሁን እንጂ ይህ የለውጥ ዋዜማ በሁለት ተፃራሪ ኃይሎች የስንግ ተይዞ በአንድ በኩል ለዴሞክራሲ መወለድ
የሚያምጡትን ያህል በሌላ በኩል የህዝባችንን የሰቆቃ ዘመን ለማራዘም በወያኔ ተላላኪነት እና ጉዳይ አስፈፃሚነት ቀን ከሌሊት በጥቅም ታውረው የሚታትሩ እንዳሉ ይታወቃል። ለዚህም በተለምዶ
"የዳያስፖራ ፖለቲካ" በመባል የሚታወቁት ከኢትዮጵያ ውጪ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ እና ድጋፍ
ሰጪ ድርጅቶች የዚሁ የወያኔ ቅጥረኞች የቀጥታ ሰለባ ሲሆኑ በተለይ በቅርቡ የግንቦት-7 ለሁለት
መከፈል በአይነቱ የሚጠቀስ ሲሆን ሌላው ሰሞኑን በሁለት ገቢር ተከፍሎ  በኢትዮጵያ ህዝብ
አርበኞች ግንባር ላይ ያነጣጠረው አሳፋሪም አስቂኝም ድራማ ነው።ስለሆነም እነዚህን ባለሁለት ገቢር
ድራማዎች በጥልቀት ማየቱ ረጅሙ የወያኔ እጅ ምን ያህል ተኩላዎችን የበግ ለምድ እያለበሰ
በውስጣችን እንደሰገሰገ ለማሳየት ይረዳል።

ገቢር-አንድ
ከኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር በተፃፈ ደብዳቤ ከድርጅቱ በስነ-ምግባር የተባረሩ ስደተኞችን
በማሰባሰብና ከጀርባ በመሆን የሃሰት ክስና የስም ማጥፋት ዘመቻ በአመራሮቹ ላይ በሰፊው እንዲደረግ
ከፍተኛ ሚና በመጫወት የመጀመሪያውን ያልተሳካ ሙከራ ያደረገው የወያኔና የሻዕቢያ ተላላኪው አቶ
በላይነህ ወንዳፍራሽ የሚባል ግለሰብ ሲሆን በአደባባይ የወያኔን መንግስት የሚቃወም ቢመስልም
በተግባር የታየው ግን ያለምንም ችግር ኢትዮጵያ የሚመላለስ ከመሆኑ ባሻገር ከስደተኞች በሚዘርፈው
ገንዘብ አዲስ አበባ ውስጥ በልጁ ስም የመድሃኒት ማከፋፈያ ድርጅት እንዳለው ይታወቃል። ከዚህም
ባሻገር ይህ ግለሰብ በጀርመን ሀገር የሲቪክ ማህበር አቋቁሚያለሁ እያለ በአንድ በኩል ከተሰማራበት
የሽንት ቤት ማፅዳት ስራ ከሚያገኘው ገቢ ታክስ እንዳይቀነስበት የዕርዳታ ድርጅት አቋቁሜ ስደተኞችን እየረዳሁ ነው በሚል ለምክንያትነት የሚጠቀምበት ሲሆን በሌላ በኩል ከስደተኞች ገንዘብ
ለመዝረፊያ ይጠቀምበታል።

ጥቂት ስለ ሲቪክ ማህበሩ
ይህ ራሱን የሲቪክ ማህበር እያለ የሚጠራ ድርጅት በላይነህ ወንዳፍራሽ  በሚባል ግለሰብ የሚመራ
ሲሆን ይህ ግለሰብ ከዛሬ 5 ዓመት በፊት ማለትም የአርበኞች ግንባር ከኤርትራ ከመውጣቱ በፊት
ከዳያስፖራ ለጋሽ ግለሰቦች ለግንባሩ የተሰበሰበውን 37000.00 ዩሮ ´´ቁማር ተበላሁ´´ በሚል ተልካሻ
ምክንያት ገንዘቡን ለግል ጥቅሙ ያዋለ ሲሆን ዛሬም ይህ የማጭበርበር ተሞክሮ አድማሱን በማስፋት
በስደተኞች ላይ የሚያደርገውን ዘረፋ በሚከተሉት መልኩ እያከናወነ ይገኛል።

1. ሰላማዊ ሰልፎችን በማዘጋጀት ለስደተኞች ማመላለሻ በሚል ከለጋሽ ድርጅቶች አውቶብሶችን
በነፃ ከተረከበ በኋላ እያንዳንዱን ስደተኛ ለትራንስፖርት 20.00 ዩሮ እና ከዛ በላይ
እንዲከፍሉ ማስገደድ።

2. ከአሜሪካና ከካናዳ የተጋበዙ እንግዶች የሚመሩት ስብሰባ ስላለ በሚል ስደተኞችን ከየከተማው
እንዲሰበሰቡ ካደረገ በኋላ ከካሪታስ በስደተኞች ስም በነፃ ለተፈቀደለት አዳራሽ የመግቢያ እና
የአዳራሽ ኪራይ ክፈሉ እያለ ስደተኞችን ለተጨማሪ ወጪና እንግልት መዳረግ።

3. ለስብሰባዎችም ሆነ ለሰላማዊ ሰልፎች የተሳትፎ የምስክር ወረቀት ልስጣችሁ በሚል በነፍስ
ወከፍ 1.50 ዩሮ ክፈሉ እያለ ስደተኞችን ማንገላታትና መበዝበዝ ይገኝበታል።

ገቢር-ሁለት /ኦክቶበር 20,2012/
 "አፉ ከእኛ፤ልቡ ከነኛ"
ይህ ድራማም የተፈፀመው በበላይ ወንዳፍራሽ በሚመራውና  በጀርመን ሀገር በሚገኘው ከማንኛውም
የፖለቲካ አመለካከት "ነፃ" የሆነ አቋም አለኝ በሚለው ማህበር ሲሆን ይህ ማህበር ፈቃዱን ሲያገኝ
በተለይ ስደተኞችን "አገለግላለሁ" በሚል እሳቤ ቢሆንም ከላይ በተጠቀሰው መሰረት የስደተኞችን
ገንዘብ መበዝበዣ ሆኖ የሚያገለግል ድርጅት ነው።ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ይህ ማህበር ምንም እንኳን
በኢትዮጵያውያን ስም የተመሰረተ ቢሆንም ኦክቶበር 20,2012 ቀን "እውነተኛው የኢትዮጵያ ህዝብ
አርበኞች ግንባር በሻዕቢያ ቁጥጥር ስር ያለው ስለሆነ ኑ በቪዲዮ ኮንፍረንስ ላረጋግጥላችሁ" ሲል
ስብሰባ ጠራ።ከዛ በፊት ግን ለግንዛቤ እንዲረዳ አንዳንድ ነጥቦችን እናንሳ።
የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር በርግጥም በአንድ ወቅት በኤርትራ ምድር ላይ ይንቀሳቀስ የነበረ
ቢሆንም በሚከተሉት ጠንካራ ምክንያቶች ከዛሬ ሁለት አመት በፊት ከጥቂት የሻዕቢያ ጉዳይ
አስፈጻሚዎች በቀር ሙሉ በሙሉ ከኤርትራ ለቆ ወደበረሃማው ሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል ወርዷል።

   1. ሻዕቢያ በኢትዮጵያ ላይ ያለው የማይቀየር አቋም፦ ሻዕቢያ በኢትዮጵያ ላይ ያለው
አቋም ዛሬ እንደአዲስ የሚነሳ ሳይሆን "የመቶ አመት የቤት ስራ" በወያኔ በኩል የሰጠን
ቢሆንም ከአመታት በኋላ ቀርበን ብናየውም ይህ አቋሙ ምንም ያልተቀየረ ሲሆን በተለይ
እንደየኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር አይነት አንድነትን የሚሰብኩ ድርጅቶች ተጠናክረው
እንዳይወጡ በመከላከል ይልቁንም ስር-ነቀል ለውጥ ከማምጣት ይልቅ በወያኔ ላይ ትንኮሳዎችን
በማድረግ ብቻ ወያኔን ከመጣል ይልቅ በመተንኮስ ላይ ብቻ እንድናተኩር ጫና በማድረጉ።  

2. ሻዕቢያ በእጅ አዙር ሊጠቀምብን በመፈለጉ፦በእርግጥም ሻዕቢያ ከመሰረታዊው
የኢትዮጵያ ህዝብ ጥቅም ይልቅ የራሱን ጦርነት በእጅ አዙር /Proxy War/ እንድንዋጋለት
በመፈለጉ እና ይህንንም በተቃወሙ አባሎቻችን ላይ የሞት እርምጃ በመውሰዱ ነው።
ወደጥንተ ነገራችን ስንመለስ የጀርመኑ "የሲቪክ" ማህበር ነው እንግዲህ በሻዕቢያ ቁጥጥር ስር
የሚገኘውን ቡድን በኢትዮጵያ ለምድ በመሸፋፈን ለኛ ለኢትዮጵውያን እንደመርገም ጨርቅ የሆነውን
የሻዕቢያ አርማ ከፍ አድርጎ ያውለበለበው።
በእርግጥ መለስ ዜናዊ ሲሞት ከወያኔ እኩል ለቅሶ የተቀመጠው ሻዕቢያ መሆኑን ላስተዋለ የወያኔ እና
የሻዕቢያ "ቅራኔ" "አህያ ቢራገጥ…….". እንደሚባለው ነውና በሻዕቢያ አጋፋሪነት የኢትዮጵያ ህዝብን
ጥቅም አስከብራለሁ ማለት ዘበት ነው።እናም ይህ "የሲቪክ" ማህበር ነው እንግዲህ በሻዕቢያ ሳምባ
እየተነፈሰ የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባርን "ለማስታረቅ" ብሎም ለመምራት ኃላፊነቱን ስጡኝ
ሲል የደፋር ድፍርስ አይኑን እያቁለጨለጨ የጠየቀው።
"ለራሱ አያውቅ ነዳይ፤ቅቤ ለመነ ለአዋይ" እንዲሉ!!!

ዘገየ አለምሰገድ ከበደ
ከስሽቱትጋርት