Saturday, March 28, 2015

የውሃ ምንነትና የተንዣበበበት አደጋ - እስክንድር ንጉሴ

የውሃ ምንነትና የተንዣበበበት አደጋ 

Eskender Negussie እስክንድር ንጉሴ


              ምድራችንን ህይወት የሚኖርባት ገነት ካደረግዋት ነገሮች አንዱ ውሃ ነው. ውሃ በሶስት አይነት ሁነታ የመገኘቱ ሚስጥር ህይወት እንዲቀጥል አድርጎታል. ስለውሃ ጥቅም ብዙ መዘርዘር ይቻላል በአጭሩ ግን ውሃ ከሌለ ህይወት የለም. ምድር 70%ቱ በውሃ የተሸፈነ ነው. ከዛ ሁሉ ውሃ ግን ጨዋማ ያልሆእው 1 ፐርሰንት ብቻ ነው.ከዚህ ሁሉ ውሃ 1% ብዙ ቢሆንም ከአለም ህዝብ ጋር ስናነጻጽረው ግን በጣም ጥቂት ነው. በተጨማሪም ከዚህ አንድ ፐርሰንት ውሃ ላይ 68% በከርሰ ምድር ውስጥ ሲገኝ፣ 31 ፐርሰንቱ ዳግሞ በበረዶ መልክ በ አርክቲክ እና በ አንታርቲካ ይገኛል. በርዶውም ሲቀልጥ ወደ ውቂያኖስ ውስት ይገባል. በዚህ መሰረት ከፍተኛውን ንጽሁ ውሃ ማግኘት አይችልም. በመሬት ወለል ላይ የሰው ልጅ በቀላሉ ሊያገኘው የሚችለው ውሃ አንድ ፐርሰንት ብቻ ነው. ይሀንንም አንድ ፐርሰንት ቀሪ ውሃ በወንዞች ላይ በመገደብ ውሃውን ወደ ጨዋማነት እንዲቀየር በማድረግ ብሎም ግድብ ወንዙ እንዲደር መንሳኤ ይሆናል፣ ለምሳሌ በሁቨር ግድብ እንደታየው  የመጠጡን ውሃ የበለጠ እንዲቀንስ ያደርገዋል. በዚህ መሰረት ግድብ መገደብ በድሮጊዜ ሰዎች የተጠቀሙበት አማራጭ ሲሆን ባለፈእርጀ ብዙ ችግሮች ሊያመጣ እንደሚችል ይታወቃል. ለምሳሌ ክግድቡ በታች ያሉትን በወዝ ውስጥ የሚገኙትን የህይወት ሰንሰለቶችን በመቆራረጥ ህይወትን ያተፋል. ከግድቡ በላይ የነበረውን ያየር ንብረት ተፈጥሮአዊ ሂደቱን በመለወጥ ያካባቢው ገባሬዎች የግብርና ስራቸውን በአግባቡ እንዳይሰሩ ያግዳቸዋል. ጉዳቱ ውሃ ውስጥ ብቻ ሳይሆን ከውሃውም ውጪ ያሉትን ህይወቶችን ይነካል. በብዙ ግድቦች ምክንያት መኖሪያቸውን ለቀው ይሚሄዱት ሰውች ብቻ ሳይሆኑ እንሥሳቶችም ናቸው. ከዚህ በፊት እንዳልነው ግድቦች ውሃው ውስጥ ያለውን የምግብ ሰንሰለት ያጠፋሉ፣ በዚህ የተነሳ በአካባቢው የሚገኙ አሳ የሚመገቡ ወፎች አካባቢውን ለቀው ይሰደዳሉ.
                 ወደ ኢትዮጵያ ስናትርኩር የውሃ ችግር ዘመናትን ያስቆጠረ ነው ነገር ግን ኢትዮጵያ የውሃ ዓንባ ስትሃኦን ህዝቦቹዋ ውሃን ሊያገኙት እልቻሉም ለምሳሌ በሃረር ከተማ ከ25 እመታት በፊት የተከሰተው እሳሳቢ የውሃ ችግር እስካሁን መፍቴ ባለማግኘቱ እስካሁን እየተገለገሉ ያሉት ውሃ በትራንስፖርት ከእለማያ ድሬደው እንዲሁ ከእካባቢው የገጠር መንደሮች በማመላለስ ሲሆን ከተማ ውስጥ በማንኛውም ሰእት ሰዎች የ ውሃ መያዣ ይዘው ውሃ ፍለጋ ሲንከራተቱ መየት የተለመደ ነው ማንኛውም እይነት መኪና ዊሃ ወደ ከተማዋ ሲያጉጉዝ ዪስተዋላል እየባሰ የመጣው የውሃ ችግር የእለማያ ሃይቅ በመድረቁ ተባብሶ ቀጥሎል ታዲያ የሃረርን ህዝብ የየጎረበት ሃገርን የመብራት ችግር የሚፈታውን የህዳሴ ግድብ ለመገንባት ቦንድ ግዛ መባሉ እዪቀርም የቱ ቅድሚ መሆን እንዳለበት ፍርዱን ለእድማጮቼ እተዋልው
               ግብጽ በየአመት ተጨማሪ 21 ቢልዮን ኩቢክሜትር ውሃ እንደምትፈልግና ማንኛውንም በወንዙ ላይ የሚካሄደውን ግንባታ በቸልተኝነት እንደማትመለከተው የሃገሪቱ ባለስልጣናት አስታወቁ. 90 ሚሊየን ህዝቡዋ ወደ 150 ሚሊየን ስለሚያድግ በውሃ ላይ ያላት አቋም ከፍተኛ እንደሆነ የመስኖው ሚኒስተሩ ሆሳም ሙግዛሪል ገለጹ. ግብጽ፣ሱዳንና ኢትዮፒያ በአባይ ውሃ ላይ ደርሰውበታል የተባለውን ፍትሃዊ አጠቃቀም በከፍተኛ ባለስልጣናት ዘንድ ዛሬ በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም ይፈራረሙበታል ተብሎ ይጠበቃል. ሃገራቱ ደርሰውበታል የተባለው ፍተሃዊ አጠቃቀም ለህዝቡ ገና ይፋ አልተደረገም. ግብጽ ከአባይ ውሃ ማግኘት የሚገባትን ያህል ውሃ እያገኘች እንዳልሆነ ሚኒስተሩ ገልጸዋል. በድርድሩ የግብጽን የውሃ ፍላጎት ለማስከበር ጥረት እንደሚያደርጉ ገልጸዋል. በአሁን ሰአት 55 ቢልየን ኩቢክሜትር ውሃ በየአመቱ እንደምታገኝ እና በቃጣይ አመታት ተጨማሪ ውሃ እንደሚያስፈልጋት መገለጽዋ ይታወሳል.

               ግብጽ ሱዳንና ኢትዮፒያ ግድቡ ይሚያስከትለውን ጉዳት የሚያጠና እለም እቀፍ ድርጅት ይፋ የማድረግ ስምምነቱ በማይታወቅ ምክንያት መራዘሙ ይታወቃል ሆኖም ዛረ ስምምነቱን ሲያጸድቁ አለም አቀፍ ድርጅቱን ይፋ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል. ኢትዮጵያ በቡድኑ ውስጥ አለም አቀፍ ባሉሙያ እንዲሳተፉ ፈቀደች. በስብሰባው ላይ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለምን አለም አቀፍ ባለሙያ እንዲካተቱት እንደፈቀዱ የሰጡት ማብራሪያ የለም.

No comments:

Post a Comment